የክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ኢኒሸቲቭ እና የከተማው...

image description
image description
image description
image description
image description
image description
image description
image description
image description
image description
- In Uncategorized    0

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ኢኒሸቲቭ እና የከተማው ዋና ዋና የትኩረት መስኮች የሰምንት ወር እቅድ ግቦች የአምስት ወር አፈፃፀም  በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ተገመገመ፡፡

ባለፉት አምስት ወራት በክፍለ ከተማው የተሰሩ የመቀነስ ግብ፣ የዜሮ ግብ፣ የአንድ ግብ፣ የሁለት እጥፍ ግብ፣ የማዝለቅ ግብ የተረጅነት ቅነሳ፣ የፕሮክት አፈፃፀም፣ የከተማ ግብርና፣ የገቢ፣ የስራ እድል ወዘተ  አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ ተገምግሟል፡፡

ባለፉት አምስት ወራት የኑሮ ውድነትን በመቀነስ እና ገበያን በማረጋጋት፣በስራ እድል ፈጠራ፣በከተማ ግብር ፣በገቢ አሰባሰብ፣ እና በሌሎች ስራዎች  ግቦቹን ለማሳካት የተሻለ ስራ እንደተሰራ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጃንጥራር  አባይ ገልጸዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በሚያደርገው ያልተቋረጠ ጥረት እንደ ስኳር፣ዘይት እና ሌሎች የፍጆታ ምርቶችን ለህብረተሰቡ በፍትሃዊነት እያቀረበ እንደሚገኝ አቶ ጃንጥራር ገልጸዋል፡፡

አቶ ጃንጥራር አክለውም  መንግስት የያዛቸውን  ግቦች  ለማሳካት አመራሩ በትኩረት መስራት እንዳለበት ገልጸው የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የምርት አቅርቦትን በመጨመር ፣የስራ እድል ፈጠራን በማሳደግ፣ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ፣መልካም አስተዳደርን በማጠናከር እና ህገ ወጥነትን በመከላከል ትኩረት በማድረግ የተጠናከረ ስራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በመጨረሻም እንደ መንግስት የታቀዱ ግቦቹን ለማሳካት በየደረጃው ያለ ሁሉም አመራር  በትኩረት መስራት እንዳለበት ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አሳስበዋል።

 


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments